ማስታወቂያ
ዜና
ማስታወቂያ
መጋቢት 30፣ 2014 (ገቢዎች ሚኒስቴር)
በገቢዎች ሚኒስቴር የምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በግብር ከፋይነት ለተመዘገባችሁ 654 ድርጅቶች በሙሉ፡-
ግብር ከፋዮች ግብር/ታክስ የማሳወቅ ግዴታ ያለባችሁ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ ማሽን ጋር በተያያዘ በህግ የተቀመጡ ግዴታዎችን ካልተወጡ በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር - 983/08 መሰረት በአስተዳደራዊና በወንጀል የሚያስቀጣ መሆኑ በህግ ተደንግጓል፡፡
በዚህም መሰረት ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘራችሁ 654 ድርጅቶች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ30 ቀናት ውስጥ ቀርባችሁ በጽሑፍ ተአማኒነት ያለውን ማስረጃ በመያዝ የድሮው ለም ሆቴል አካባቢ የሚገኘው ኮሜት ህንጻ ቁጥር 2 ቀርባችሁ በድርጅቱና በስማችሁ የተመዘገበውን የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ ያለበትን ሁኔታ እንድታሳውቁ እየገለጽን ግዴታችሁን ካልተወጣችሁ ግን በታክስ አስተዳደር አዋጁ ላይ በተቀመጠው የሕግ ድንጋጌ መሰረት የአስተዳደራዊ ቅጣትና የወንጀል ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን እናሳስባለን፡፡
በገቢዎች ሚኒስቴር የምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት