ደረሰኝ ሳይዙ ሸቀጦችን ጭነው በሚንቀሳቀሱት ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው

Nested Applications

Asset Publisher

null ደረሰኝ ሳይዙ ሸቀጦችን ጭነው በሚንቀሳቀሱት ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው

የታክስ ሕጉ ማንኛውም ነጋዴ ወይም አገልግሎት ሰጪ ግብይት ካከናወነ በኋላ ደረሰኝ እንዲቆርጥ ቢያስገድድም ደረሰኝ የማይሰጡ እያጋጠሙ በመሆኑ የገቢዎች ሚኒስቴር እርምጃ ሊወስድ እንደሆነ በሚኒስቴር /ቤቱ የታክስ ማጭበርበርና ምርመራ ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ ገዙ አስታወቁ፡፡

አንድ ዕቃ ወይም አገልግሎት ሽያጭ በሚከናወንበት ጊዜ የተጨማሪ እሴት ታክስን 15 በመቶ ጨምሮ ከገዢው ወይም ከተጠቃሚው ለመንግስት ታክስ እንዲሰበስብ በሕጉ ውክልና መሰጠቱን ኃላፊው አስረድተዋል፡፡ ይሁንና በሀገራችን አገልግሎት ሰጪም ሆኑ በየደረጃው ያሉ የንግዱ ማህበረሰብ የታክስ ሕጉን ተከትለው እንደሚሠሩ ሁሉ ደረሰኝ የማይሰጡ መኖራቸውን አቶ ሲሳይ ጠቁመዋል፡፡

ከነዚህ መካከል ሸቀጦች እና ንብረቶች የሚያጓጉዙ እና ጫኝ ድርጅቶች መሆናቸውን ጠቅሰው ሸቀጥ ከመጫናቸው በፊት ሕጋዊ ሰነድ መኖርና አለመኖሩን እያረጋገጡ መሄድ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡ ይህንኑ ተቋሙ ወደ እርምጃ ከመግባቱ በፊት በማስታወቂያ እና በሌሎች የማስተማሪያ መንገዶች የማስገንዘብ ሥራ እንደሚሠራ አመልክተዋል፡፡ ሁሉም ክልሎች በዚህ ላይ በትኩረት እንዲሠሩ አቅጣጫ ለመስጠት መታሰቡን ጠቅሰው በየትኛውም ደረጃ ያሉ የሕግ አስከባሪ አካላት ጭነቶች በሚጓጓዙበት ጊዜ ህጋዊ ሰነድ መያዛቸውን እንዲያረጋግጡ እንደሚደረግም አብራርተዋል፡፡

በታክስ ሕጉ መሰረት አንድ ጭነት ሕጋዊ ሰነድ ሳይኖረው ሲንቀሳቀስ ከተያዘ በዋናነት የጭነቱ ባለቤት ሸቀጡን ከየት እንዳመጣ ማስረጃ መስጠት ያለበት ሲሆን ይህ ሳይሆን ሲቀር ወደ ኋላ በመሄድ ሸቀጡን ያለደረሰኝ የሸጠው አካል ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እና የሕግ ተጠያቂነት እንደሚያስከትልበት አስታውቀዋል፡፡

Asset Publisher

ዜና

  • የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ Fri, 29 Mar 2024
የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ
  • በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል Mon, 18 Mar 2024
በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል
  • የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ Fri, 15 Mar 2024
የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ

Asset Publisher

Untitled Basic Web Content

Nested Applications

Asset Publisher

.