የገቢዎች ሚኒስቴር የሁሉም ክልሎች የገቢ ዘርፍ አመራሮች በታክስ ምንነት፣ ህጎችና አዋጆች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና
የገቢዎች ሚኒስቴር የሁሉም ክልሎች የገቢ ዘርፍ አመራሮች በታክስ ምንነት፣ ህጎችና አዋጆች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል ተሰጥቷል፡፡
በስልጠናው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት በሚኒስትር መ/ቤቱ የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ለጀመረችው ሀገራዊ የገቢ ዕድገት ወጥ የሆነ የታክስ ግንዛቤ መያዝ እጅግ ወሳኝ ነው፡፡ በክልሎች የገቢውን ዘርፍ የሚመሩ የስራ ኃላፊዎች በክልል ደረጃ ለያዙትም ይሁን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተያዘው እቅድ በታክስ ዙሪያ ያለቸውን ግንዛቤና እውቀት ማዳበር ይገባቸዋልም ብለዋል፡፡ አመራሮቹ በስልጠናው ላይ በሚኖራቸው ጊዜም የተሻለ የታክስ አረዳድና ግንዛቤ እንደሚይዙ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡
በስልጠናው ላይ ከሁሉም ክልሎች የገቢው ዘርፍ አመራሮች በተጨማሪ የሚኒስቴር መ/ቤቱ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በብዛት የተነበቡ ዜናዎች
-
Fri, 29 Oct 2021"ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው
"ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው
-
Wed, 4 Jan 2023"የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ተግተን እንሰራለን " ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)