Asset Publisher

ዜና

  • የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ Fri, 29 Mar 2024
የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ
  • በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል Mon, 18 Mar 2024
በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል
  • የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ Fri, 15 Mar 2024
የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ

Most Viewed Assets

null "የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ተግተን እንሰራለን " ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)

የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ እና የጉምሩክ ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ የኮምቦልቻ ጉምሩክ እና ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱ ማጠቃለያ የስራ መመሪያ የሰጡት የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ፣ የኮምቦልቻ ገቢዎች እና ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በደረሰባቸው ውድመት ከመቆዘም ወጥተው በፍጥነት ወደ ስራ መግባታቸው አመራሩ እና ሰራተኛው ለለውጥ ያለውን ቁርጠኝነት እና ትጋት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሯ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ያቀድነውን ብቻ ሳይሆን ካቀድነው በላይ ለመፈጸም እንሰራለንም ብለዋል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በበኩላቸው፣ ሁለቱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ በሚካሄድበት አካባቢ የሚገኙ በመሆናቸው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በብቃት መሰብሰብ የሚያስችል ፈጣን እና የደንበኞችን ፍላጎት የሚያረካ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡

ያለን አማራጭ ልማት እና ብልጽግና ብቻ ነው ያሉት ኮሚሽነር ደበሌ፤ ይህን እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ዘመን ተሻጋሪ ስራዎችን መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል::

በአካባቢው ተፈጥሮ በነበረው ጦርነት የኮምቦልቻ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት እንደነበር ያስታወሱት የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራአስኪያጅ አቶ ሰማን ዳውድ፣ አመራሩ እና ሰራተኛው በደረሰው ውድመት ሳይደናገጥ በርትቶ በመስራቱ አሁንላይ የተሻለ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የስራ ከባቢን መፍጠር እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡