የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ

Nested Applications

Asset Publisher

የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ

የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ Fri, 29 Mar 2024

በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል

በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል Mon, 18 Mar 2024

የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ

የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ Fri, 15 Mar 2024

የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት Thu, 29 Feb 2024

Asset Publisher

null የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ

መጋቢት 19/2016 . (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የታክስ ሰርዓቱን ለማዘመን የወረቀት አሰራሮችን የሚያስቀር  የኤሌክትሮኒክስ ኢንቮይስ ሲስተም አስተዳደር  ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል ሰነድ  ከከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት  አስተዳደር ጋር ተፈራርሟል::

ስምምነቱን  የገቢዎች ሚኒስትር / አይናለም ንጉሴ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት  አስተዳደር  ዋና ዳይሬክተር / ትግስት ሀሚድ ፈርመዋል::

በስምምነቱ ላይ የገቢዎች ሚኒስትር / አይናለም ንጉሴ  በህገ ወጥ ንግድ በቀረጥ እና ታክስ ማጭበርበር ምክንያት የኢትዮጽያ ኢኮኖሚ መሰብሰብ ያለበትን ገቢ ለመሰብሰብ አለመቻሉን አመላክተው ይህ ስርዓት  የግብይት ደረሰኝን ከአንድ አካል ብቻ ማለትም ከገቢዎች ሚኒስቴር ብቻ እንዲቆረጥ በማድረግ በሃሰተኛ ደረሰኝ የሚደረግ ማጭበርበርን የሚያስቀር ነው ብለዋል::

ሚኒስትሯ  ስርዓቱ ለነጋዴው ማሕበረሰብም ሆነ ለሸማቹ ከፍተኛ ጥቅም የሚሰጥ እንደሆነ ተናግረው የነጋዴው ማህበረሰብ ለደረሰኝ ሕትመት የሚያወጣውን ወጪና ጊዜ ከማስቀረቱም በላይ የግብይት ሂደቱን በቀጥታ ለመከታተልና ለመቆጣጠርም እንደሚያስችል ገልፀዋል፡፡

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት  አስተዳደር  ዋና ዳይሬክተር / ትግስት ሀሚድ በበኩላቸው የሚዘረጋው  የኤሌክትሮኒክስ ኢንቮይስ ሲስተም  ስርዓት የማንዋል የደረሰኝ አስተዳደር ስርአት ወደኤሌክትሮኒክስ የደረሰኝ አስተዳደር ስርአት ለመቀየር የሚያስችል እንዲሁም የዲጂታል ግብይት ስርአቱን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳልጥ   መሆኑን አንስተው የሚዘረጋው ስርዓት ውጤታማ እንዲሆን የተቻለው ጥረት ሁሉ እንደሚደረግም ተናግረዋል::

Asset Publisher

Untitled Basic Web Content

Nested Applications

Asset Publisher

.