የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ስኬታማ ለማድረግ እንደሚሰራ ተገለጸ

Nested Applications

Asset Publisher

null የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ስኬታማ ለማድረግ እንደሚሰራ ተገለጸ

ሐምሌ 18/2016 . (የገቢዎች ሚኒስቴር)

 

በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ስርዓት ዘርፍ 2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና 2017 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ውይይት እያካሔደ ይገኛል።

 

በመድረኩ የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ስርዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ቱሉ እንዳሉት 2016 በጀት ዓመት እቅድ ከባለፉት ዓመታት አንጻር ከፍተኛ ቢሆንም በገቢ አሰባሰብ ጥሩ አፈጻጸም ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ ለእቅዱ መሳካትም ከሁሉም ሰራተኛ ውጤታማ እርብርብ በተጨማሪ አስቻይ ሁኔታዎችን በሚገባ መለየት መቻሉ፣ ተቋማዊ ሪፎርም ተጠናክሮ መሰራቱ፣ የሕግ ማስከበር ስራው ውጤታማ መሆኑ፣ የታክስ እና ጉምሩክ ንቅናቄ በትኩረት መሰራቱ ውጤታማ የታክስ አሰባስብ እንዲኖር ጉልህ ሚና ነበረው ብለዋል።

 

አያይዘውም 2017 በጀት ዓመት እቅድን ማሳካት የሚቻለው በዋነኝነት የሁሉም የተቋሙ ሰራተኛ ርብርብ ሲኖር መሆኑን በመገንዘብ አመራሩ እና ፈጻሚው በእቅዱ ላይ በንቃት ተወያይቶ የጋራ እቋም በመያዝ ውጤታማ እንደሚያደርግ ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልጸዋል።

 

በመድረኩ ላይ በሚኒስቴሩ የታክስ ስርዓት ዘርፍ አማካሪ አቶ ሂካ ባርባ የዘርፉን 2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፓርት ለውይይት አቅርበዋል።

Asset Publisher

ዜና

  • በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ512 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል Wed, 31 Jul 2024
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ512 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል
  • የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ስኬታማ ለማድረግ እንደሚሰራ ተገለጸ Wed, 31 Jul 2024
የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ስኬታማ ለማድረግ እንደሚሰራ ተገለጸ
  • ማስታወቂያ Sat, 18 May 2024
ማስታወቂያ

Asset Publisher

Untitled Basic Web Content

Nested Applications

Asset Publisher

.