Asset Publisher

null የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ስኬታማ ለማድረግ እንደሚሰራ ተገለጸ

ሐምሌ 18/2016 . (የገቢዎች ሚኒስቴር)

 

በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ስርዓት ዘርፍ 2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና 2017 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ውይይት እያካሔደ ይገኛል።

 

በመድረኩ የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ስርዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋዬ ቱሉ እንዳሉት 2016 በጀት ዓመት እቅድ ከባለፉት ዓመታት አንጻር ከፍተኛ ቢሆንም በገቢ አሰባሰብ ጥሩ አፈጻጸም ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ ለእቅዱ መሳካትም ከሁሉም ሰራተኛ ውጤታማ እርብርብ በተጨማሪ አስቻይ ሁኔታዎችን በሚገባ መለየት መቻሉ፣ ተቋማዊ ሪፎርም ተጠናክሮ መሰራቱ፣ የሕግ ማስከበር ስራው ውጤታማ መሆኑ፣ የታክስ እና ጉምሩክ ንቅናቄ በትኩረት መሰራቱ ውጤታማ የታክስ አሰባስብ እንዲኖር ጉልህ ሚና ነበረው ብለዋል።

 

አያይዘውም 2017 በጀት ዓመት እቅድን ማሳካት የሚቻለው በዋነኝነት የሁሉም የተቋሙ ሰራተኛ ርብርብ ሲኖር መሆኑን በመገንዘብ አመራሩ እና ፈጻሚው በእቅዱ ላይ በንቃት ተወያይቶ የጋራ እቋም በመያዝ ውጤታማ እንደሚያደርግ ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልጸዋል።

 

በመድረኩ ላይ በሚኒስቴሩ የታክስ ስርዓት ዘርፍ አማካሪ አቶ ሂካ ባርባ የዘርፉን 2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፓርት ለውይይት አቅርበዋል።

Most Viewed Assets

በብዛት የተነበቡ ዜናዎች

  • "ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው Fri, 29 Oct 2021
"ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው
  • "የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ተግተን እንሰራለን " ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር) Wed, 4 Jan 2023
"የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ተግተን እንሰራለን " ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)