በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ512 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል
ሐምሌ 21/ 2016 ዓ.ም (ገቢዎች ሚኒስቴር)
የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን በ2016 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ በአርባምንጭ ከተማ ውይይት በማካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡
በመድረኩ በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት 529.3 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ512 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰብ መቻሉን የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ ገልጸዋል፡፡
ከአምናው በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር ገቢው ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለውም ገልፀዋል፡፡
ሚኒስትሯ አክለውም ዘመናዊ እና ተደራሽ የታክስና የጉምሩክ አስተዳደር ስርዓትን በመገንባት አዳዲስ አሰራሮችን በመቅረፅ እንዲሁም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመደገፍ ገቢ አሰባሰቡን ውጤታማ በማድረግ የዕቅዱን ከ96 በመቶ በላይ እንዲሳካ አስችሏል ብለዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ህገወጥ ንግድ እና ኮንትሮባንድ በሀገራዊ የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱ ላይ የጎላ ተፅዕኖ እንዳሳረፈ ገልፀው፤ በቀጣይ በጀት ዓመት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ህጋዊነትን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ትብብር እንዲያደርጉ ሚኒስትሯ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በብዛት የተነበቡ ዜናዎች
-
Fri, 29 Oct 2021"ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው
"ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው
-
Wed, 4 Jan 2023"የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ተግተን እንሰራለን " ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)